Jan 31, 2025 .
የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት እና ዋፋ ማርኬቲንግ እና ፕሮሞሽን በጋራ በሚሰሩባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያዩ፡፡

የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት እና ዋፋ ማርኬቲንግ እና ፕሮሞሽን በጋራ በሚሰሩባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያዩ፡፡
የተወያዩት የምክር ቤቱ ዋና ጸሐፊ ዶክተር ቀነኒሳ ለሚ እና የዋፋ ማርኬቲንግ እና ፕሮሞሽን ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ፋንታዬ ጌታነህ ናቸው፡፡
ሁለቱ ተቋማት በተለይም ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ኩነቶችን በትብብር እና በጋራ በማዘጋጀት የኢትዮጵያን ምርትና አገልግሎት ማስተዋወቅ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ነው የተወያዩት፡፡ ሁለቱ ተቋማት በጋራ በሚሰሩባቸው ጉዳዮች ዙሪያ የመግባቢያ ስምምነት እንደሚፈራረሙም በውይይቱ ወቅት ተጠቁሟል፡፡

